Staff Profile

የዕፅዋት ት/ት ክፍል ተልዕኮ፣ ራዕይ እና እሴቶች

  • ተልዕኮ

በሀገራዊ የትኩረት አቅጣጫ መሠረት ፈጣንና ዘላቂ እድገት ማምጣት የሚችል ጥራት  ተደራሽና አግባብነት ያለው ትምህርት በመስጠት ዲሞክራሲያዊ ባህልን የተላበሰና ኃላፊነት የሚሰማው ዜጋ ማፍራት፡፡

  • ራዕይ

በ2027 ዓ.ም ከምስራቅ አፍሪካ ግንባር ቀደም  10 ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ካሉት የዕፅዋት ሳይንስ ት/ት ክፍሎች መካከል በትምህርት ጥራት፤ በልማታዊ ምርምር አንዱ መሆን ፡፡

  • እሴቶቻችን
  1. ቅድሚያ ለተማሪ፡ ተማሪዎቻችን የት/ት ክፍሉን ህልውና የሚወስኑ፤ጠቀሜታውን ማሳያና የጥንካሬያችን ምንጭ መሆናቸውን እናምናለን፡፡
  2. ጥራት ያለው ትምህርት፡ ማንኛውም ተግባሮቻችን መለኪያቸው የትምህርት ልቀት ሞሆን እንዳለበት እናምናለን፡፡
  3. አካዳሚክ ነጻነት እና ተጠያቂነት፡ ተጠያቂነትን ያገናዘበ የትምህርት ነፃነት ለማስፈን እንሰራለን፡፡
  4. ተወዳዳሪነትና ፈጠራ፡ የሰራተኛዎቻችንን አቅም በማጎልበት የተወዳዳሪነትና የፈጠራ አቅማችንን ለማረጋገጥ እንተጋለን፡፡
  5. ወጪ ቆጣቢነትና ውጤታማነት፡ ምንጊዜም ቢሆን አዳዲስ ምንገዶችን በመተግበር በአነስተ ወጪ ምርታማነታችንን ለማረጋገጥ እንሰራለን፡፡
  6. በጋራ የመስራት ባህል፡ የሰራተኞቻችን ተሳትፎ የህይወት መንገዳችን ነው፡፡ ስለሆነም በጋራ በመስራት የእርስ በርስ መከባበርና መተማመንን እናጎለብታለን፡፡
  7. ለስነ-ምግባር መገዛት፡ ማንኛውም ተግባሮቻችን ከዩኒቨርሲቲው ህግና መመሪያ ፣ እንዲሁም ተቀባይነት ያላቸውን የዩኒቨርሲቲና የማሁበረሰቡን ደንቦች ጋር የተዛመደ መሆን እንዳለበት እናምናለን፡፡

Staff Profile